በአንድነት ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት እናደርጋታለን። እድገት፣ ፈጠራ እና የህዝቦቿ ደህንነት ግንባር ቀደም ናቸው። የኢትዮጵያን ብሩህ የወደፊት ተስፋ በመቅረጽ እና የትውልድ ህልሞችን እውን ለማድረግ እኛን ይቀላቀሉን።
የፕላንና ልማት ቢሮ ለክልላዊ እቅድ እና ልማት ተቀዳሚ የመንግስት ተቋም እንደመሆኑ መጠን የደቡብ ክልል ቀጣይነት ያለው እድገት እና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ በመቅረፅ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ሁሉን አቀፍ ልማትን የሚያራምዱ እና የደቡብ ህዝብ ህይወት የሚያሻሽሉ ውጤታማ ስትራቴጂዎችን፣ ፖሊሲዎችን እና ፕሮግራሞችን ለመንደፍ እና ተግባራዊ ለማድረግ በቁርጠኝነትና በትጋት ይሰራል።
ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል አሰራርን በማዘመን ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ የሀብት አጠቃቀም ከክልሉ መካከለኛና ረጅም ጊዜ ዕቅድ ጋር ያለውን ተመጋጋቢነት ማረጋገጥ፤
የክልሉን የረጅም፣ የመካከለኛና የአጭር ጊዜ ዕቅድ ለማዘጋጀት የሚዉሉ የልማት መረጃዎች በየአስተዳደር እርከኑ እንዲሰበሰቡ ያደርጋል፤አፈፃፀማቸውን ይከታተላል፤ ይገመግማል::
በክልሉ ሁለገብ ልማት ላይ አስፈላጊውን የፖሊሲ ትንተና፣ መመሪያ እና ድጋፍ ለመስጠት። የዘርፍ ሃላፊዎችን እና የሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት በማስተባበር የመካከለኛና የረዥም ጊዜ ሀገራዊ ልማት እቅድ ማዘጋጀት። የመንግስት ኢንቨስትመንት አስተዳደር እና አስተዳደር ብቃትን ለማዳበር ፖሊሲዎችን፣ ፕሮግራሞችን እና የልማት ፕሮጀክቶችን ቀልጣፋ ግምገማ፣ መምረጥ እና ቅድሚያ መስጠት።
የቢሮ ሃላፈ
የልማት መረጃና ስነ-ህዝብ ጉዳዮች ዘርፍ ሃላፊ
ማክሮ ኢኮኖሚ ዕቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዘርፍ ሃላፊ
Project Manager
የክልሉን የረጅም፣ የመካከለኛና የአጭር ጊዜ ዕቅድ ያዘጋጃል፤ አፈፃፀማቸውን ይከታተላል፤ ይገመግማል፤ ሪፖርት በማዘጋጀት ለሚመለከታቸው አካላት ያቀርባል፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቀፍ ያዘጋጃል፤ ለመስተዳድር ምክር ቤት አቅርቦ ያስፀድቃል፤ የክልሉን መንግሥት የካፒታል ፕሮጀክቶች የአዋጪነት ጥናት ያካሂዳል፤ ይገመግማል፤ ያስፀድቃል፤ የክልሉ የታችኛው የአስተዳደር እርከን ዓመታዊ የሀብት ማከፋፈያ ቀመር ያዘጋጃል፤ ለክልሉ ምክር ቤት እንዲፀድቅ ያቀርባል፤ የክልሉን የካፒታል ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ክትትልና ግምገማ ያደፈርጋል፤ ወቅታዊ ሪፖርት በማዘጋጀት አግባብነት ላላቸው አካላት ያቀርባል፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ አፈፃፀም ጥናት ያካሂዳል፤ የክልሉን የልማት ክፍተት እና የመልማት አቅም ጥናት ያደርጋል፤
የክልሉን የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና መልክዓ ምድራዊ መረጃዎችን ይሰበስባል፤ ያደራጃል፤ ትንተና በማድረግ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ያደርጋል፤
የክልሉን የስታቲስቲክስና መረጃ ሥርዓት በማዘመን ለመንግስታዊ መስሪያ ቤቶች ድጋፍ ይሰጣል፤ ሥራውን ያስተባብራል፤ ይመራል፤
የሥነ ህዝብ ጉዳዮችን በልማት ዕቅድ አካቶ ከመተግበር አኳያ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ያስተባብራል፤
የክልሉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ስርጭትንና የመልክዓ ምድራዊ ገጽታን የሚያሳይ አትላስና ካርታ ያዘጋጃል፤